ዜናዎች

የተቋሙ ስልጣንና ተግባራት

.የአሶሳ ከተማ አስ/ረ የወረዳ ሁለት ን/ኢ/ት ጽ/ቤት ሥልጣንና ተግባራት፡-

  1. ንግድ፣ እንዲስፋፋ የተመቻቹ ሁኔታዎች እንዲፈጠሩ ያደርጋል፤
  2. የወረዳችን ንግድን ለማስፋፋትና ለማጠናከር ቀልጣፋ የግብይት ሥርዓትና ተገቢ የንግድ አሠራር እንዲሰፍን ያደርጋል፤
  3. አግባብ ባለዉ ሕግ መሠረት የንግድ ምዝገባና ፈቃድ አገልግሎት ይሰጣል፣ ፣ ይሰርዛል፣ የንግድ መዝገብ ያደራጃል፤
  4. ተገቢ ያልሆኑ የንግድ አሠራር ለመከላከል የሚያስችል የተሟላ ሥርዓት ይዘረጋል፣የንግድ ህጎች መከበራቸዉን ያረጋግጣል፣ አፈፃፀማቸዉን ይከታተላል፤
  5. በህጉ መሠረት ለሸማቾች ጥበቃ ያደርጋል፣ የንግድ ዕቃዎችንና ሥርጭት ይቆጣጠራል፤
  6. በወረዳችን የዋጋ ተመን ላይ ክትትልና ቁጥጥር ያደርጋል፤
  7. የወረዳችን ህጋዊ ሥነ-ልክ ሥርዓት በአግባቡ መተግበሩን ክትትልና ቁጥጥር ያደርጋል
  8. በወረዳችን የትራንስፖርት ህጎች እንዲከበሩ ክትትልና ቁጥጥር ያደርጋል
  9. በወረዳችን የታሪፍና የፌርማታ ቁጥጥርና ክትትል ያደርጋል
  10. በወረዳዉ የመንገድ ትራንስፖርት ህጎች መከበራቸዉን ይከታተላል፣ እርምጃ ይወስዳል፤
  11.  አሽከርካሪ ተሸከርካሪዎችን ይቆጣጠራል አስፈላጊውን እርምጃ ይወሰዳል
  12.  በማኑፋክቸሪንግ ኢንዱስትሪዎች እንዲስፋፉ ምቹ ሁኔታዎችን በመፍጠር ድጋፍና ክትትል ያደርጋል
  13.  ከከተማ እናሌሎች ባለድርሻ አካላት ጋር የመንገድ ትራፊክ አደጋ ለመከላከል በቅንጅት ይሰራል፣ በወረዳችን የመንገድ ትራንስፖርት እንዲሳለጥ ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል
  14.  ዓላማዉን ለማስፈፀም የሚችሉ ሌሎች ተዛማጅ ተግባራትን ያከናዉናል፡