ዜናዎች

ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ ያደረጉ ና ያለአግባብ ምርት ያከማቹ የንግድ ድርጅቶችን እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ መቀጠሉን የወረዳ ሁለት ንግድ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ወሊድ አንዋር አስታወቀ::

ነሐሴ 07/2016 የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት ንግድ ጽ/ቤት፤

የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት ንግድ ጽ/ቤት የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያው ተግባራዊ ከተደረገበት ጊዜ ጀምሮ በወረዳው የተቋቋመው የንግድ ቁጥጥር የጋራ ግብረሃይል 1052 የንግድ ተቋማት ላይ የተደረገው ክትትል ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ያደረጉና ምርት በማከማቸት በድምሩ 45 የንግድ ድርጅቶችን በማሸግ 3 ታስረው እንዲጠየቁ መደረጉን ኃላፊው ገልፃዋል።

ያልተገባ የዋጋ ጭማሪና የምርት ክምችት የሚያደርጉ ስግብግብ ነጋዴዎች ላይ እየተወሰደ ተጠናክሮ የሚቀጥል በመሆኑ ህብረተሰቡ ህገ-ወጥ የንግድ እንቅስቃሴ ሲያጋጥመው አቅራቢያው ላለው የንግድ ተቋም ጥቆማ በመስጠት እንዲሁም የግብረሀይል ተቆጣጣሪዎች የስልክ መስመር +251917709817/ +251 91 340 4416 ደውሎ ጥቆማ በመስጠት ሕገ-ወጥ ንግድ እንዲከላከል የጽ/ቤቱ ኃላፊ አሳስበዋል ፡፡

ዘገባው የአሶሳ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት ንግድ ጽ/ቤት

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *